መግቢያ
የኢትዮጵያ
ብሔራዊ ምርጫ
ቦርድ በፌደራላዊና
ክልላዊ መንግስታት
ገለልተኛ፣ ነጻና
የማያደሉ ምርጫዎች
ለማካሄድ እራሱን
የቻለ አካል ሆኖ
በ1985 ዓ.ም ተመሠረተ፡፡
ቦርዱ
አስፈላጊ ደንብና
መመሪያዎችን
የማዉጣት፣ የምርጫ
አስፈጻሚዎችን
መመደብ እና ማሰልጠን፣
ምርጫዉን በሚመለከት
የሥነ ዜጋ ትምህርቶችን
ለህብረተሰቡ
መስጠት፣ የምርጫ
ዉጤቶችን ማረጋገጠና
ዉጤቶቹን የማሳወቅ
ሀላፊነት አለበት፡፡
ቦርዱ
በምርጫ ጊዜ የሚፈጠሩ
መስተጓጉሎችን
የማረምና የሚቀርቡለትን
አቤቱታዎችን
የመመርመር ስልጣን
አለዉ፡፡ በምርጫ
ሂደት ጊዜ የደንብና
መመርያዎች መተላለፎች
ከተፈጸሙ፣ ወይም
የማታለል ወይም
ሰላምን የማደፍረስ
ደርጊቶች በምርጫ
ላይ መስተጓጉሎችን
እስኪፈጥሩ ድረስ
ከተጋነኑ፣ የምርጫ
ቦርዱ የምርጫ
ዉጤቶችን የመሰረዝ
እና አዲስ ምርጫዎች
እንዲካሄዱ የማዘዝ
ሀይል አለዉ፡፡
ቦርዱ
በተጨማሪ ስታትስቲካዊ
መረጃዎችን በመሰብሰብና
በማጥናት እንደ
አስፈላጊነቱ
ለፓርላመንት
የምርጫዉን ሂደት
በሚመለከት ማሻሻያዎችን
ያቀርባል፡፡
የኢትዮጵያ
ብሔራዊ ምርጫ
ቦርድ በብሔራዊና
በክልል ደረጃ
በሚካሄዱ ምርጫዎች፣
እንዲሁም የዞን፣
የወረዳ፣ እና
የቀበሌ ምክር
ቤት ምርጫዎችን፣
የምትክ ተወካዮችን
ምርጫን፣ በድጋሚ
እነዲከናወኑ
የተደረጉ ምርጫዎችን፣
ሪፈረንደሞችን
የማስተዳደር
ሀላፊነት አለዉ፡፡
የኢትዮጵያ
ብሔራዊ ምርጫ
ቦርድ ተግባራትና
ስልጣን በ1986 ህገ
መንግሰት ዉስጥ
እና በአዋጅ ቁጥር
111/1987 እንዲሁም በማሻሻያዉ
አዋጅ ቁጥር 438/1997
ላይ ሰፍሯል፡፡