Top Banner
Site Map Links Contact Us
Home
Election Day Countdown
About NEBE
What's New
Electoral System
Legal Framework
Electoral Operations
Maps & Data
Domestic & International Observers
Election Results
Photo Gallery
 
ስለ ብሔራዊ ምርጫ ቦርዱ  
 
መግቢያ | ምርጫ ቦርድ አባላት |ምርጫ ቦርድ አባላት የትምህርት መረጃ ታሪክ | ምርጫ ቦርድ አደረጃጀት
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አባላት የትምህርት መረጃ ታሪ

የቦርዱ ሊቀመንበር
_____________________________________________________________

አቶ ከማል በድሩ ኬሎ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከህዳር 1985 ዓ.ም.ጀምሮ በሊቀመንበርነት እያገለገለሉ ነዉ፡፡ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚደንትም ናቸዉ፡፡ ይህንንም ስልጣን ለ13 አመታት ይዘዋል፡፡ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከመግባታቸዉ በፊት አቶ ከማል የከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኛ ሆነዉ ለአራት አመት ሰርተዋል፡፡ በዉጭ ጉዳይ ሚኒሰቴር ዉስጥም ለበርካታ አመታት አገልግለዋል፡፡

አቶ ከማል በአሁኑ ግዜ የህገ መንግስት አጣሪ ጉባኤ፣ ማለትም በህገ መንግስቱ ዙሪያ የሚነሱ ክርክሮችን የሚያጣራና ወሳኔዉን ለፌደሬሽን ምክር ቤት የሚያስተላልፈዉ አካል ፕሬዚደንት ናቸዉ፡፡ አቶ ከማል የሀረር ክልል ተወላጅ ሲሆኑ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህግ ዲግሪ አላቸዉ፡፡

አቶ ከማል በድሩ ኬሎ
የቦርዱ አባላት___________________________________________________________________

አቶ አብደላ አደም በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከ ህዳር 1985 ዓ.ም. ጀምሮ አገልግለዋል፡፡

ላለፉት 28 አመታት የራሳቸዉን የሂሳብ ስራ ድርጅት ሲመሩ ቆይተዋል፡፡ በራሳቸዉ ድርጅት መስራት ከመጀመራቸዉ በፊት አቶ አብደላ በገንዘብ ሚንስቴር በአገር ዉስጥ ገቢ ክፍል ዉስጥ ኦዲተርና የሂሳብ ክፍል ሀላፊ ሆነዉ አገልግለዋል፡፡

በመንግሰተ ኢንዱስትሪ ዘርፍም በኮስት አካዉንቲንግ ስራ የብዙ አመት ልምድም አላቸዉ፡፡ ከሀርቫርድ ዩኒቨርሲቲ በህዝብ አስተዳደር የማስተርስ ዲግሪና ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በኢኖሚክስ የባችለር ዲግሪአላቸዉ፡፡ አቶ አብደላ የተወለዱት በትግራይ ክልል ነዉ፡፡

አቶ አብደላ አደም


አቶ ግርማ ጃርሶ ወደ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የገቡት በህዳር 1985 ዓ.ም. ነዉ፡፡ አቶ ግርማ በመንግስት ድርጅቶች ዉስጥ በተለያዩ የጥናትና የንግድ ክፍሎች በሀላፊነት ለ21 አመታት አገልግለዋል፡፡

በአሁኑ ግዜ አቶ ግርማ ጃርሶ የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱሰትሪ ድርጅት የግዢ ሀላፊ ናቸዉ፡፡ አቶ ግርማ የተወለዱት በደቡብ ክልል ሲሆን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ 1976 ዓ.ም በስታትስቲክስ ዲግሪ አላቸዉ፡፡

 

 
አቶ ግርማ ጃርሶ
 

ወ/ሮ ከበደች እርዳቸዉ ማሙዬ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከሐምሌ 1991 ጀምሮ እያገለገሉ ይገኛሉ፡፡ ወ/ሮ ከበደች የኢኮኖሚና የባህል ማስፋòያ ድርጅት ስራ አስኪያጅ ናቸዉ፡፡ በኢትዮጵያ ንግድ ምክር ቤት ዉስጥ ለ28 አመታት ያገለገሉ ሲሆን፣ በንግድ ምክር ቤቱ ወደ መጨረሻ ቆይታቸዉ የኤግዚቢሽን ከፍተኛ ባለሙያ ሆነዉ አገልግለዋል፡፡

ወ/ሮ ከበደች እርዳቸዉ በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ በወጪ ንግድ ስራ ላይ የተሰማሩ ሴቶች ፎረም ፕሬዝደንት እና በኢትዮጵያ በንግድና በልዩ ልዩ ሙያ የተሰማሩ ሴቶች ማህበር ምክትል ፕሬዝደንት እንዲሁም የኢትዮጵያ ህግ ባለሙያ ሴቶች ማህበር ተባባሪ አባል ናቸዉ፡፡

ወ/ሮ ከበደች ከ1985 እስከ 1987 ድረስ በተቀመጠዉ የህገ መንግስት አርቃቂ ኮሚሽን አባል ሆነዉ ሰርተዋል፡፡ ወ/ሮ ከበደች አክሽን ፎር ዴቨሎፕመንት ለተባለዉ መንግስታዊ ላልሆነ ድርጅት መሥራች እና አባል ናቸዉ፡፡ ወ/ሮ ከበደች የተወለዱት በአዲስ አበባ ነዉ፡፡

 

ወ/ሮ ከበደች እርዳቸዉ
 
   
 
 
     
   
Pages   1| 2|