ዕጩ ተወዳዳሪዎች
ማንኛዉም
የተመዘገበ መራጭ
የሚከተሉትን
ነጥቦች ካሟላ
ዕጩ ተወዳዳሪ
ሊሆን ይችላል፡፡
•
ኢትዮጵያዊ፣
•
ሊወዳደሩበት ያሰቡበትን
ክልል ቋንቋ መናገር
መቻል፣
•
በምርጫዉ ቀን ቢያንስ
21 የሆነዉ/የሆናት፣
ሊወዳደሩበት
ባሰቡበት የምርጫ
ክልል ከምርጫ
ቀን ቀደም ብሎ
በነዋሪነት ለሁለት
ዓመት የቆዩ ወይም
ለመወዳደር ባሰቡበት
ወረዳ ወይም ከተማ
የተወለዱ መሆን
አለባቸዉ፡፡
የግል
ተወዳዳሪዎች
በምርጫ ቀበሌዉ
ለመምረጥ ብቁ
ከሆኑ ነዋሪዎች
1000 የድጋፍ ፊርማዎችን
መሰብሰብ አለባቸዉ፡፡
በፖለቲካ ድርጅቶች
የሚቀርቡ ተወዳዳሪዎች
ለመመዝገብ የድጋፍ
ፊርማዎችን መሰብሰብ
አይጠበቅባቸዉም፡፡
የተመዘገቡ ዕጩ
ተወዳዳሪዎች
የመወዳደሪያ
ምልክታቸዉን
እራሳቸዉ መምረጥ
ይችላሉ፡፡ የፓርቲ
ምልክቶች ባለቤትነት
በቦርዱ የተረጋገጠ
ነዉ፡፡
ከ35
የፖለቲካ ፓርቲዎች
የተዉጣጡ ተወዳዳሪዎች
እንዲሁም 353 የግል
ተወዳዳሪዎች
በጠቅላላዉ 1845 ተወዳዳሪዎች
ለሕዝብ ተወካዮች
ምክር ቤት መቀመጫዎች
ለመወዳደር ተመዝግበዋል፡፡
ከ33 የፖለቲካ ፓርቲዎች
የተዉጣጡ ተወዳዳሪዎች
እንዲሁም 70 የግል
ተወዳዳሪዎች
በጠቅላላዉ 3662 ተወዳዳሪዎች
ለክልል ምክር
ቤት መቀመጫዎች
ይወዳደራሉ፡፡