የኢትዮጵያ
ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ
መንግስት የታወጀዉ
ህዳር 30 1986ዓ.ም ስራ
ላይ በዋለዉ ህገመንግስት
ስር ነዉ፡፡ ይህ
የዘጠኝ ነጻና
በከፊል ራሳቸዉን
ችለዉ የሚተዳደሩ፣
የሕዝብ አሰፋፈራቸዉ
ቋንቋ፣ ማንነት
እና ፈቃድ ላይ
መሰረት በማድረግ
የተዋቀሩና አዲስ
አበባን መዐከል
ያደርጉ ብሔራዊ
ክልሎች ፌደሬሽን
ነዉ፡፡ የፌደሬሽኑ
መንግስት አባላት፡
ትግራይ፣ አፋር፣
አማራ፣ ኦሮሚያ፣
ሶማልያ፣ ቤንሻንጉል/ጉሙዝ፣
ጋምቤላ፣ ሐረር
እና የደቡብ ክልል
ብሔር፣ ብሔረቦችና
ሕዝቦች ክልል
ናቸዉ፡፡ የሀገሪቱ
ህዝብ ብዛት 72.4 ሚልዮን
ሲሆን የቆዳ ስፋቷ
1.13 ስክዌር ኪሎሜትር
(437,794 ስክዌር
ማይል) ነዉ፡፡
ህገመንግስቱ የመድበለ
ፓርላመንታዊ
ሥርዓትን ያቋቋመ
ሲሆን፣ በስሩም
ሁለት ምክር ቤቶች
ማለትም የሕዝብ
ተወካዮች ምክር
ቤት እና የፌደሬሽን
ምክር ቤትን ይይዛል፡፡
የሕዝብ ተወካዮች
ምክር ቤት
የሕዝብ ተወካዮች
ምክር ቤት በፌደራሉ
መንግስት ከፍተኛዉን
ስልጣን ሲይዝ
ሁሉንም የፌደራል
ጉዳዮች አስመልክቶ
ህግ የማዉጣት
ሀይል ያለዉ፡፡
የሕዝብ ተወካዮች
ምክር ቤት አባላት፤
ሁሉን አቀፍ፣
ነፃ፣ ቀጥተኛ፣
ትክክለኛ በሆነ፣
ድምፅ በሚስጥር
በሚሰጥበት ሥርዓት
በየአምስት ዓመቱ
በሕዝቡ ይመረጣሉ፡፡
የምክር ቤቱ አባላት
በአንድ የምርጫ
ክልል ዉስጥ ከሌሎች
ተወዳዳሪዎች
መካከል አብላጫ
ድምፅ ያገኘ ተወዳዳሪ
አሸናፊ በሚሆንበት
የምርጫ ሥርዓት
ይመረጣሉ፡፡
የምክር ቤቱ አባላት
ቁጥር የሕዝብ
ብዛትንና በልዩ
ትኩረት ዉክልና
የሚሰጣቸዉ አናሳ
ብሔረሰቦችና
ሕዝኖችን ቁጥር
መሰረት በማድረግ
በአሁኑ ጊዜ 547 ሲሆኖ
ከዚህ ዉስጥ አናሳ
ብሔረሰቦች 22 መቀመጫ
ይኖራቸዋል፡፡
ጠቃላይ ሚሊስትሩ
ከሕዝብ ተወካዮች
ምክር ቤት አባላት
መካከል ይመረጣሉ፡፡
በሕዝብ ተወካዮች
ምክር ቤት አብላጫ
መቀመጫ ያገኘዉ
የፖለቲካ ድርጅት
ወይም ያገኙት
ጣምራ የፖለቲካ
ድርጅቶች የመንግስትን
ሥልጣን ይረከባል/ይረከባሉ፡፡