የፌደሬሽን ምክር
ቤት
በህገመንግስቱ ስር
110 መቀመጫ ያለዉ
የፌደሬሽኑ ምክር
ቤት በፌደራሉ
መንግስት አባል
ክልሎች የሚገኙት
ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች፣
ሕዝቦች የሚልኩዋቸዉ
አባላት የሚወከሉበት
ምክር ቤት ነዉ፡፡
እያንዳንዱ ብሔር፣
ብሔረሰብ፣ ሕዝብ
ቢያንስ አንድ
ተወካይ ይኖረዋል፤
በተጨማሪም የብሔር
ወይም ብሔረሰቡ
አንድ ሚሊዮን
ህዝብ አንድ ተጨማሪ
ወኪል ይኖረዋል፡፡
የፌደሬሽን ምክር
ቤት አባላት በክልል
ምክር ቤቶች ይመረጣሉ፤
የክልል ምክር
ቤቶች በራሳቸዉ
ወይም በሕዝብ
በቀጥታ እንዲመረጡ
በማድረግ የፌደሬሽን
ምክር ቤት አባል
እንዲወከል ያደርጋሉ፡፡
ይህ አሠራር በተግባር
ላይ ዉሎ አያዉቅም፡፡
በክልል ደረጃም
የፌደሬሽን ምክር
ቤት ተወካዮችን
ቀጥተኛ ምርጫዎችን
የማድረግ ህግ
አልቀረበም፡፡
ሁለቱ በፌደራል መንግስት
ምክር ቤቶች የፌደሬሽኑን
ፕሬዚደንት ማለትም
የኢትዮጵያ ፌደራላዊ
ዴሞክራሲያዊ
ሪፐብሊክ ርዕሰ
ብሔርን በጋራ
ይመርጣሉ፡፡
ፕሬዚደንቱ በዋናነት
የሚኖራቸዉ የክብር
ስልጣን ሲሆን
የሥራ ዘመናቸዉ
ስድስት አመት
ይሆናል፡፡
በአስተዳደር ደረጃ
የኢትዮጵያ ዘጠኝ
መንግስታት በ70
ዞኖች ይከፈላሉ፡፡
ዞኖቹም ከ600 ወረዳዎች
የተዋቀሩ ሲሆኑ
በግምት በ28,000 መንደሮች ይከፈላል፡፡
ህገመንግስቱ
እስከ 550 የቀበሌ
ምራጫዎች ሊኖሩ
እንደሚችል ቢያስቀምጥም
በግዜዉ ያሉት
ግን 547 ናቸዉ፡፡
የክልል ምክር
ቤቶች
የዘጠኙ ክልሎችና
የአዲስ አበባ
አስተዳደር የክልል
ምክር ቤቶች ምርጫዎችም
የሚካሄዱት አብላጫ
ድምፅ ያገኘ ተወዳዳሪ
አሸናፊ በሚሆንበት
የምርጫ ሥርዓት
ነዉ፡፡ ነገር
ግን ከአንድ የምርጫ
ክልል ከእንድ
በላይ ተወዳዳሪዎች
ሊመረጡ ይችላሉ፡፡
የእያንዳንዱ
የምርጫ ክልል
የመቀመጫ ብዛት
የሚወሰነዉ በኢትዮጵያ
ብሔራዊ ምርጫ
ቦርድ ሲሆን የክልላዊ
ህገመንግስቶች
ወይም ህጎችን
መሰረት በማድረግ
ነዉ፡፡ በአሁኑ
ግዜ ያለዉ በየክልሎች
የሚገኘዉ የመቀመጫ
ብዛት እንደሚከተለዉ
ነዉ፡፡ በአዲስ
አበባ 6፣ በትግራይ
4፣ በአማራ 2፣ በኦሮሚያ
3፣ በሶማሊያ 3፣
በቤንሻንጉል/ጉሙዝ
10፣ በደቡብ ክልል
ብሔር ብሔረቦች
መንግስት 3 መቀመጫዎች፣
በጋምቤላና በሐረር
የምርጫ ቀበሌዎች
በየግዜዉ በቁጥር
የሚለያዩ መቀመጫዎች
አላቸዉ፡፡