Top Banner
Site Map Links Contact Us
Home
 
ስለ ብሔራዊ ምርጫ ቦርዱ
Election Day Countdown
መግቢያ | ምርጫ ቦርድ አባላት |ምርጫ ቦርድ አባላት የትምህርት መረጃ ታሪክ | ምርጫ ቦርድ አደረጃጀት

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አባላት

ቦርዱ የተዋቀረዉ ጠቅላይ ሚኒሰትሩ በሚያቀርቧቸዉ፣ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሚሾሙ ሰባት አባላት ሲሆን አባላቱም ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነዉ፡፡

የቦርድ አባላት የሚመረጡት ለህገ መንግስቱ ያላቸዉን አክብሮት፣ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ግንኙነት የሌላዉ መሆኑንና የስራ ብቃታቸዉን መሠረት በማድረግ ነዉ፡፡

የቦርዱ ሊቀመንበር የሚመረጠዉ በተወካዮች ምክር ቤት ሲሆን ለቦርዱ ጠቅላላ አስተዳደርና እንቅስቃሴ ሀላፊነት ይኖራቸዋል፡፡

የቦርዱ ምክትል ሊቀመንበር የሚመረጠዉ ከአባላቶቹ መካከል ሲሆን ሊቀመንበሩ በማይኖሩበት ግዜ ሥራቸዉን ይሰራል፡፡

ቦርዱ ስራ አስፈጻሚና በምክትል ስራ አስፈጻሚ የሚመራ ጽህፈት ቤት ይኖረዋል፡፡ ሁለቱም የሚመረጡት በስራ ልምዳቸዉና በችሎታቸዉ ነዉ፡፡ በጠቅላይ ሚኒሰትሩ ጥቆማ በተወካዮች ምክር ቤት ሊመረጡም ይችላሉ፡፡ ስራ አስፈጻሚዉ የመምረጥ መበት የሌለዉ የቦርዱ አባልና የቦርዱ ሴክረተሪያትም ሆኖ ያገለግላል፡፡

የቦርዱ አባላት በስራ አፈጻጸማቸዉ ገለልተኛና እራሳቸዉን የቻሉ የሙያ ሰዎች ናቸዉ፡፡

የቦርድ ዉሳኔዎች የሚወሰኑት በአብላጫ ድምጽ ነዉ፡፡ አቻ ዉጤት በሚኖርበት ግዜ የቦርዱ ሊቀመንበር ወሳኙን ምርጫ ያደርጋል፡፡ ቦርዱ በየሳምንቱ ስብሰባ የሚያደርግ ሲሆን ስብሰባዉን ለማስኬድ የሚያስፈልገዉ ኮረም የአራት አባላት መሟላት ይሆናል፡፡

 

About NEBE    
What's New    
Electoral System    
Legal Framework    
Electoral Operations    
Maps & Data    
Domestic & International Observers    
Election Results    
Photo Gallery    
       
     
     
 
 
This site is designed by Afrolink Studio
Copyright © 2005 National Electoral Board of Ethiopia. All rights reserved.