Top Banner
Site Map Links Contact Us
Home
Election Day Countdown
About NEBE
What's New
Electoral System
Legal Framework
Electoral Operations
Maps & Data
Domestic & International Observers
Election Results
Photo Gallery
 
   
 

የፕሬስ መግለጫ (ሚያዝያ 18 ቀን 1997 ዓ ም)

ቦርዱ 20,000 የምርጫ ማረጋገጫ ቀለም ተረከበ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ በመጪው ምርጫ የመራጮችን የአውራ ጣት ለመቀባት የሚያገለግል 20000 የድምፅ ሰጪዎች ማረጋገጫ ቀለም ተረከበ፡፡ ለምርጫው በአጠቃላይ የሚያስፈልገው 240,000 ቀለም ሲሆን ቀሪው በሳምንት ጊዜ ተጠናቆ እንደሚገባ ይጠበቃል፡፡

በሕንድ ኩባንያ አማካኝነት ተገዝቶ እየገባ ያለው አዲሱ ቀለም ከዚህ በፊት ተገዝቶ ቶሎ የሚለቅ በመሆኑ ጥቅም ላይ እንዳይውል በተወሰለው ቀለም የተተካ ነው፡፡

የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ከማል በድሪ እንደገለፁት ከዚህ በፊት ተገዝቶ የነበረው ቀለም 12 በመቶ የሲልቨር ናይትሬት ይዘት ሲኖረው የአሁኑ ግን 25 በመቶ ሲልቨር ናይትሬት የያዘ ነው ብለዋል፡፡ ይህም ቀለሙ ቶሎ እንዳይለቅ ያደርገዋል ተብሏል፡፡

ለቀለሙ ግዥ የሚያስፈልገው ወጪ ለመጪው ምርጫ ለጋሾች በሰጡት ገንዘብ የተሸፈነ ሲሆን አዲሱን ቀለም ያስመጣው ኩባንያ ቀለሙን ለቀየረበት ተጨማሪ ወጪ አልጠየቀም፡፡

አዲሱ ቀለም በፖ­ርቲዎች የጋራ መድረክ ተቀባይነትን አግኝቷል፡፡ የጋራ መድረኩ ከዚህ በፊት የተገዛውን ቀለም ቶሎ የሚለቅ በመሆኑ ሥራ ላይ እንዳይውል መጠየቁ ይታወሳል፡፡

 

 
     
     
       
           
     
 
 
This site is designed by Afrolink Studio
Copyright © 2005 National Electoral Board of Ethiopia. All rights reserved.