Top Banner
Site Map Links Contact Us
Home
Election Day Countdown
About NEBE
What's New
Electoral System
Legal Framework
Electoral Operations
Maps & Data
Domestic & International Observers
Election Results
Photo Gallery
 
   
 

የፕሬስ መግለጫ (ሚያዝያ 19 ቀን 1997 ዓ ም)

ለምርጫ አስፈፀሚዎች ሥልጠና ተሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ በመጪው ምርጫ ተግባራዊ የሚደረጉ አዳዲስ አሰራሮችን በተመለከተ ለምርጫ ክልል ምርጫ አስፈፃሚዎች የሁለት ቀናት ሥልጠና ስጠ፡፡ ጥራቸው 180 የሚሆኑ የምርጫ ክልል አስፈፃሚዎች በመጀመሪያው ዙር ሥልጠና የተሳተፉ ሲሆን ቀሪዎቹም በቀጣዮቹ ሦስት ዙሮች ሥልጠናውን ይወስዳሉ፡፡

የቦርዱ ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ተስፋዬ መንገሻ እንደገለፁት የሥልጠናው ዋና ዓላማ ከዚህ በፊት በተሰጡ ሥልጠናዎች ያልተሸፈኑ ከድምፅ አሰጣጥ፣ ቆጠራና ውጤት አገላለፅ ጋር በተያያዙ ጉዳዩች ላይ አስፈፃሚዎች ግንዛቤ እንዲኖራቸው ለማድረግ ነው፡፡

በሥልጠናው በየምርጫ ጣቢያው ስለሚመደቡ ሁለት ተጨማሪ የምርጫ አስፈፃሚዎች አመላመል፣ ሥልጣናና ምደባ ገለፃ የተደረገ ሲሆን የምርጫውን ምስጢራዊነት ለመጠበቅ ያስችላል ተብሎ የታመነበት በድምፅ መስጫ ወረቀት ጀርባ ስለሚደረገው ባለ ቁጥር ማሕተም አጠቃቀም ማብራሪያ ተሰጥቷል፡፡

የምርጫ ክልል የምርጫ አስፈፃሚዎች በሥራቸው ያሉትን የምርጫ ጣቢያ አስፈፃሚዎች ተመልሰው ያሰለጥናሉ፡፡

በአገሪቱ የሶማሌ ክልልን ጨምሮ ከ100,000-120,000 ሕዝብ ያላቸው 547 የምርጫ ክልሎች ይገኛሉ፡፡

 

 
     
     
       
           
     
 
 
This site is designed by Afrolink Studio
Copyright © 2005 National Electoral Board of Ethiopia. All rights reserved.