Top Banner
Site Map Links Contact Us
Home
Election Day Countdown
About NEBE
What's New
Electoral System
Legal Framework
Electoral Operations
Maps & Data
Domestic & International Observers
Election Results
Photo Gallery
 
   
 

ሚያዝያ 25 ቀን 1997 ዓ.ም.

319አለም አቀፍ ታዛቢዎች ምርጫውን ይታዘባሉ

በኢትዮጵያ ግንቦት 7 ቀን 1997 ዓ.ም. የሚካሄደውን የፌዴራልና የክልል ምክር ቤቶች ምርጫ ለመታዘብ 319የውጭ ታዛቢዎች እንደሚሰማሩ የኢትዮጵያ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ አስታወቀ፡፡

የቦርዱ ሰብሳቢ አቶ ከማል በድሪ ባለፈው ሰኞ (ሚያዝያ 24) ለጋዜጠኞች እንደገለፁት አብዛኞቹ ታዛቢዎች ከአውሮፓ ሕብረት፣ የካርተር ማዕከል፣ አፍሪካ ሕብረትና ዓረብ ሊግ የተውጣጡ ሲሆኑ ቀሪዎች ከተለያዩ ሀገራትና ኤምባሲዎች የተወከሉ ናቸው፡፡

ታዛቢዎቻቸውን ከሚያሰማሩ አገራት መካከል ዩናይትድ ስቴትስ፣ ሕንድ፣ ቻይና፣ ጃፓንና ቱርክ ይገኙበታል፡፡  እነዚህ አገራት ታዛቢዎቻቸውን የሚያሰማሩት በኢትዮጵያ መንግሥት በተደረገላቸው ጥሪ መሆኑንም አቶ ከማል ጨምረው ገልፀዋል፡፡

የሀገር ውስጥ ታዛቢዎችን ለምን ከለከላችሁ ተብለው የተጠየቁት ሰብሳቢው ቦርዱ የሀገር ውስጥ ታዛቢዎችን እንዳልከለከለ ነገር ግን ምርጫውን ለመታዘብ ለሚፈልጉ የሀገር ውስጥ ድርጅቶች በምርጫ ሕጉ መሠረት መመሪያ ማውጣቱን ጠቁመዋል፡፡

በመመሪያው መሠረት አንድ የሀገር ውስጥ ታዛቢ ድርጅት ገለልተኛ መሆንና ድርጅቱ ሲመሰረት ምርጫን መታዘብ እንደ አንድ አላማው ያስቀመጠ መሆን ይኖርበታል፡፡

የጋዜጠኞችን የፈቃድ አሰጣጥ በተመለከተ በሕጉ መሠረት ጋዜጠኛ መሆናቸው በማስታወቂያ ሚኒስቴር ሲረጋገጥ ቦርዱ በምርጫ ጣቢያዎች መዘገብ የሚያስችላቸውን ፈቃድ ይሰጣቸዋል ብለዋል፡፡

በፖለቲካ ፓርቲዎች የሚቀርቡ ቅሬታዎችን አፈታት በተመለከተ ለቀረበላቸው ጥያቄ መልስ ሲሰጡ ቦርዱ እስከአሁን ሲቀርቡለት ለነበሩና እየቀረቡለት ላሉ አቤቱታዎች በየደረጃው በተቋቋሙ የፖለቲካ ፓርቲዎች መድረኮችና ከዋናው መሥሪያ ቤት አጣሪ ቡድን በመላክ ችግሩን ከመረመረ በኋላ መፍትሔ እየሰጠ ይገኛል ብለዋል፡፡

ከተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች በቀረቡ ጥቆማዎች አማካኝነት ከምርጫ ሕጉ ውጭ ሲሰሩ የተገኙ የምርጫ አስፈፃሚዎች ከሥራ እንዲሰናበቱና በሕግ እንዲጠየቁ እየተደረገ መሆኑንም አቶ ከማል አብራርተዋል፡፡

 

 
     
     
       
           
     
 
 
This site is designed by Afrolink Studio
Copyright © 2005 National Electoral Board of Ethiopia. All rights reserved.