ግንቦት 7 ቀን
1997 ዓ.ም.
ብዛት ያላቸው
መራጮች ድምፅ ሰጡ
ለሕዝብ ተወካዮች
ምክር ቤትና ለክልል
ምክር ቤት አባላት
ምርጫ በመላው ሀገሪቱ
ከሚገኙ መራጮች
ብዙዎቹ ወደምርጫ
ጣቢያዎች ሄደው
ድምፃቸውን እንደሰጡ
የብሔራዊ የምርጫ
ቦርድ ጽሕፈት ቤት
ሊቀመንበር አቶ
ከማል በድሪ ገለፁ፡፡
በተጨማሪም የምርጫ
ሂደቱ በሰላማዊና
በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ
እንዳለና፣ እስካሁን
ክብደት ያለው ችግር
ለቦርዱ ጽሕፈት
ቤት እንዳልቀረበ
ገልፀዋል፡፡
በመጀመሪያው ሰዓታት
ላይ የምርጫ ሂደቱ
የተጓተተ ቢሆንም
አሁን ባለው ሁኔታ
ግን ሂደቱ እየተፋጠነ
መሆኑን ገልፀዋል፡፡
“የምርጫ አስፈፃሚዎች
ተጨማሪ ሚስጢራዊ
የድምፅ መስጫ ክፍሎችን
በማዘጋጀት ሂደቱን
አፍጥነውታል፡፡”
ብለዋል፡፡
ማንኛውም ከ12፡00 ሰዓት
በፊት በምርጫ ጣቢያ
ግቢ ውስጥም ሆነ
ውጪ የተሰለፈ መራጭ
የመምረጥ መብት
እንደሚኖረው አያይዘው
ገልፀዋል፡፡
ለበለጠ መረጃ ፕሬስ
ኦፊሰር ፡- ጌታሁን አሞኝ
09643736
ረዳት ፕሬስ ኦፊሰር
፡
ሕይወት አለማየሁ
09487576
|