መጋቢት
8 ቀን 1997 ዓ.ም
ከ 26.2 ሚሊዮን
በላይ ሕዝብ በመራጭነት
ተመዘገበ
በመጪው ግንቦት
7 ቀን በሚካሄደው
አገራዊና ክልላዊ
ምርጫ ለመሳተፍ
ሕዝብ
መመዝገቡን የኢትዮጵያ
ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
አስታወቀ፡፡
ማንኛውም
የተመዘገበ መራጭ
በድምፅ መስጫው
ዕለት ስሙ፣ የትውልድ
ቦታው፣ የምርጫ
ጣቢያውን፣ የምዝገባ
ቁጥሩንና ፊርማውን
የያዘውን የመራጮች
መታወቂያ ካርድ
ይዞ መቅረብ እንደሚገባው
ቦርዱ አሳስቧል፡፡
የሶማሌ ክልልን ሳይጨምር
በመላ ሀገሪቱ የተመዘገቡ
መራጮች ስማቸው
በመራጮች መዝገብ
ላይ የሰፈረ ሲሆን
የስም ዝርዝሩ በዚህ
መዝገብ ላይ ያልሰፈረ
ማንኛውም ሰው የመምረጥ
መብት እንደማይኖረው
ተገልጿል፡፡
ከዚህ በላይ የተገለፀው
ቁጥር የሶማሌ ክልልን
የማይጨምር ሲሆን
በሶማሌ ክልል በ23
ምርጫ ክልሎች የሚገኙ
መራጮች ድምፅ የሚሰጡት
በነሐሴ 15 ቀን 1997 ዓ.ም
ይሆናል፡፡
የሶማሌ ክልል የምርጫ
ጊዜን ማስተላለፍ
ያስፈለገበት ዋናው
ምክንያት በክልሉ
የሚገኙ ነዋሪዎች
አርብቶ አደርና
ከቦታ ቦታ የሚንቀሳቀሱ
በመሆናቸው ቦርዱ
ባለው የሰው ኃይልና
የቁሳቁስ አቅም
ከሌላው የአገሪቱ
ምርጫ ጋር በአንድ
ጊዜ ማካሄድ ስለማይችል
መሆኑ በዚሁ ጊዜ
ተብራርቷል፡፡