መጋቢት
19 ቀን 1997
የኢትዮጵያ
ብሔራዊ የምርጫ
ቦርድ ዌብሳይትና
የፕሬስና ኢንፎርሜሽን
ክፍል ይፋ አደረገ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ
የምርጫ ቦርድ በመጪዉ
ግንቦት 7 ቀን 1997 ዓ.ም
ስለሚካሄደዉ ምርጫ
ለሕብረተሰቡ በቂ
መረጃ ለመስጠት
እንዲያስችለዉ
(www.electionsethiopia.org)
በሚል ስያሜ ዌብ
ሳይት ይፋ አደረገ፡፡
ይህንኑ ጥረት ይበልጥ
ለማገዝም በቦርዱ
ጽሕፈት ቤት የፕሬስና
ኢንፎርሜሽን ክፍል
ከፍቷል፡፡
የቦርዱ ዌብሳይት
የብሔራዊ ምርጫ
ቦርድን አደረጃጀትና
አሰራር፣ ልዩ ልዩ
አዋጆችና ደንቦች
እንዲሁም የቦርዱን
የዕለት ተዕለት
እንቅስቃሴ የሚገልጹ
መረጃዎችን የያዘ
ነዉ፡፡
አዲስ የተከፈተዉ
የፕሬስና ኢንፎርሜሽን
ክፍልም ቦርዱን
የሚመለከቱ የሚዲያ
ጉዳዮችን በዋነኝነት
የሚያስተናግድ
ሲሆን ለአገር ዉስጠና
ለዉጭ ጋዜጠኞች
መደበኛ የሆኑ የፕሬስ
ኮንፍረንሶችን
ያዘጋጃል፡፡