Top Banner
Site Map Links Contact Us
Home
Election Day Countdown
About NEBE
What's New
Electoral System
Legal Framework
Electoral Operations
Maps & Data
Domestic & International Observers
Election Results
Photo Gallery
 
   
 

የምርጫ ቦርድ የቅንጅት አባል ድርጅቶች ላደረጉት ውህደት እውቅና አልሰጠም

ጥቅምት 17 ቀን 1997 ..

ቅንጅት ለአንድነትና
ለዲሞክራሲ በአዲስ መልክ አደረኩ ያለውን ውህደት ሕጋዊ ዕውቅና በተመለከተ የመገናኛ ብዙሀንና ሌሎችም አካላት ማብራሪያ እንዲሰጣቸው ቦርዱን በተደጋጋሚ ጠይቀዋል፡፡  በዚህም መሠረት ቦርዱ የቅንጅቱን አመሠራረትና የአዲሱን ፓርቲ እውቅና በተመለከተ ማብራሪያ ለመስጠት ተገዷል፡፡

የኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ አንድነት ፓርቲ - መድሕን (ኢዴአፓ-መድሕን) የመላው ኢትየጵያውያን አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ቀስተደመና ኢትየጵያ ለዲሞክራሲና ማሕበረሰባዊ ፍትሕ ንቅናቄና የኢትዮጵያውያን ዲሞክራሲያዊ ሊግ (ኢዴሊ) ለግንቦት 7 ምርጫ በአንድነት ለመንቀሳቀስ እንዲችሉ ቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ በሚል ስያሜ እወቅና እንዲሰጣቸው ጥቅምት 29 ቀን 1997 .. ለቦርዱ ባቀረቡት ማመልከቻና የመመስረቻ ሰነድ ጠይቀዋል፡፡  በመመስረቻ ሰነዱ አንቀጽ 9 በግልፅ እንደተመለከተው አራቱ ፓርቲዎች የፈጠሩት ቅንጅት ለንግቦት 7 ቀን 1997 .. የሕዝብ ተወካዮችና የክልል ምክር ቤቶች አባላት ምርጫ ጊዜ ብቻ የሚያገለግል ሆኖ የእያንዳንዱ ፓርቲ ሕጋዊ ሰውነት እንደተጠበቀ የሚቆይ ነው፡፡

በዚህም መሠረት የኢትዮጵያ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ ታህሣሥ 8 ቀን 1997 .. ለቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ የዕውቅና የምስክር ወረቀት ሰጥቷል፡፡  ይሁን እንጂ በአሁኑ ወቅት የምርጫው ሂደት የቋጨ በመሆኑ ቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ የተሰጠው የዕወቅና ጊዜ አብቅቷል፡፡

ቦርዱ የቅንጅት አራቱ አባል ድርጅቶች በቅርቡ ውህደት ስለመፈፀማቸው እንደማንኛውም ሰው በመገናኛ ብዙሃን ከመስማት በስተቀር ለውህደቱ ሕጋዊ እውቅና ለማግኘት የቀረበለት ጥያቄም ሆነ የሰጠው የሕጋዊ ሰውነት ማጋገጫ የምስክር ወረቀት የለም፡፡  የተጠቀሱት ፓርቲዎች ውህደት ፈፅመው ከሆነ በሕጉ መሠረት ቀደም ሲል እያንዳንዳቸው የወሰዱትን የሕጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት በመመለስ ለአዲሱ ፓርቲ እውቅና ማመልከት ሲኖርባቸው ይህንን አላደጉም፡፡

ስለዚህም በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ የሚያውቃቸው ከላይ የተጠቀሱትን አራት የፖለቲካ ድርጅቶች በየራሳቸው ሕጋዊ ሰውነት መሆኑን እየገለፀ ከዚህ በኋላ ቦርዱ የሚኖረው ግንኙነትም ከነዚሁ አራት ፓርቲዎች ጋር ብቻ ይሆናል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ ጽሕፈት ቤት

ጥቅምት 17 ቀን 1997 ..

አዲስ አበባ፣

ለበለጠ መረጃ በእነዚህ ቁጥሮች ይደውሉ፡፡

የፕሬስ ኦፊሰር ጌታሁን አሞኘ   251 - 9 - 643738

ረዳት ፕሬስ ኦፊሰር ሕይወት አለማየሁ 251 - 9 - 487576

 
     
     
       
             
 
 
This site is designed by Afrolink Studio
Copyright © 2005 National Electoral Board of Ethiopia. All rights reserved.