Top Banner
Site Map Links Contact Us
Home
Election Day Countdown
About NEBE
What's New
Electoral System
Legal Framework
Electoral Operations
Maps & Data
Domestic & International Observers
Election Results
Photo Gallery
 
   
 

ለፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ለጥምረቶች እና ለግል ተወዳዳሪዎች ድጋፍ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በግንቦት 7፣ 1997 ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሚደረገዉ ምርጫ ለሚወዳደሩ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ጥምረቶችና የግል ተወዳዳሪዎች ድጋፍ ያደርጋል፡፡

ፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ጥምረቶች

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የምርጫ ቅስቀሳን በተመለከተ ፖለቲካ ፓርቲዎች ወይም ጥምረቶች በዕቃና በአገልግሎት የተመደበላቸውን የብር መጠን የሚጠቀሙበት ቀመር አዘጋጅቷል፡፡ ዕቃዎቹና አገልግሎቶቹ የተገዙት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በፖለቲካ ፓርቲዎች ወይም ጥምረቶች ስም ነዉ፡፡ ቀመሩ ለፖለቲካ ፓርቲዎች ወይም ጥምረቶች መጋቢት 9 ቀን፣ 1997 ዓ.ም. ቀን ተነግሯል፡፡

የብር መጠን በተወዳዳሪ፤የፖለቲካ ፓርቲ ወይም ጥምረት በተወዳዳሪ 3460 ብር ተመድቦለታል፡፡ የፖለቲካ ፓርቲ ወይም ጥምረት (75 ተወዳዳሪዎች ካሉት) በጠቅላላዉ 259500 ብር ሊቀበሉ ይችላሉ፡፡

ከአንድ በላይ ክልል ወስጥ ለሚወዳደሩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ወይም ጥምረቶች ተጨማሪ ድጋፍ፤ እያንዳንዱ ከአንድ በላይ ክልል ዉስጥ የሚወዳደር የፖለቲካ ፓርቲ ወይም ጥምረት (በእያንዳንዱ ክልል ውስጥ ከአንድ በላይ ተወዳዳሪ ያለው) በእያንዳንዱ በሚወዳደርበት ክልል የተመደበለትን 43250 ብር ይቀበላል፡፡

ሴት ተወዳዳሪዎችን ለሚያቀርብ የፖለቲካ ፓርቲ ወይም ጥምረት ተጨማሪ ድጋፍ፤ እያንዳንዱ ሴት ተወዳዳሪ የሚያቀርብ የፖለቲካ ፓርቲ ወይም ጥምረት በእያንዳንዱ የሴት ተወዳዳሪ የተመደበለትን 2160 ብር ይቀበላል፡፡

ማንኛዉም የተመደበለትን ብር ያልተጠቀመ የፖለቲካ ፓርቲ ወይም ጥምረት ከጧቱ 3፡00 ሰዓት እስከ ቀኑ 7፡00 ሰዓት በ09 429932 መደወል ይኖርበታል፡፡

የግል ተወዳዳሪዎች

እያንዳንዱ የግል ተወዳዳሪ የተመደበለትን 3460 ብር የሚደርስ የህትመት ስራ ከሶስት ማተሚያ ቤቶች በብሔራዊ የምርጫ ቦርድ በተወሰነው በአንዱ ይከናወናል፡፡

የተመደበላቸውን ገንዘብ ለመጠቀም የሚፈልጉ የግል ተወዳዳሪዎች ከሰኞ እስከ አርብ ከጧቱ 3፡00 ሰዓት እስከ ቀኑ 7፡00 ሰዓት ድረስ በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሕንፃ ሐ፣ ቢሮ ቁጥር 9   ተገኝተው መጠየቅ አለባቸው፡፡

እስከ ሚያዝያ 21፣ 1997 ከቀኑ 7፡00 ሰዓት ድረስ የተመደበለትን ገንዘብ የማይጠቀም ማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ፣ ጥምረት ወይም የግል ተወዳዳሪ ዕድሉን ያጣል፡፡

ለፖለቲካ ፓረቲዎች፣ ለጥምረቶች እና ለሁሉም የግል ተወዳዳሪዎች የተመደበው የገንዘብ መጠን እንደሚከተለው ነው፤

ለግል እጩ ተወዳዳሪዎች

ጠቅላላ
የተመደበው
 የብር
መጠን (ብር)

1,266,630

የፖለቲካ ፓርቲው / የጥምር ፓርቲው /  ስም

ጠቅላላ
የተመደበው
 የብር
መጠን (ብር)

ቅንጅት ለአንድነት እና ዴሞክራሲ

614,150

የኢትዮጵያ ዴሞክራሲዊ  ኃይሎቸ ሕብረት

410,875

የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር

767,685

የመላው ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ

192,460

የአርጎባ ብሔረሰብ ዴሞክራሲዊ ድርጅት

6,920

የአርጎባ ሕዝቦች ዴሞክራሲዊ ንቅናቄ

3,460

የአፋር ብሔራዊ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ

29,840

የአፋር አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት ግንባር

29,840

የአፋር ነፃ አውጪ ግንባር ፓርቲ

6,920

የኦሮሞ አቦ ነፃነት ግንባር

38,060

የኦሮሞ ነፃነት አንድነት ግንባር

52,765

የገዳ ስርዓት አራማጅ ፓርቲ  

151,375

የኦሮሚያ ነፃነት ብሔራዊ ፓርቲ

121,100

የኦሮሞ ፌደራሊስት ዴሞክራቲክ ንቅናቄ

295,400

ኢትዮጵያ ማህበረ-ዴሞክራሲ ፌደራላዊ ፓርቲ

3,460

ትግሪ ወርጂ ብሔረሰብ ዴሞክራሲያዊ አንድነት ፓርቲ

73,100

የቤንሻንጉልና ጉሙዝ ሕዝቦች ዴሞክራሲዊ አንድነት

24,220

የሲዳማ አርነት ንቅናቄ

67,900

የሲዳማ ሀዲቾ ህዝብ ዲሞክራሲያዊ ድርጅት

67,900

የሸኮና መዠንገር ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ግንባር

129,315

የወላይታ ሕዝብ ዴሞክራሲዊ ግንባር

32,000

የኢትዮጵያ ፓን አፍሪካኒስት ፓርቲ

61,845

የደንጣ ፣ ዱባሞ ክችንችላ ዴሞክራሲዊ ድርጅት   

6,920

የደቡብ ኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ኃይሎች አንድነት

6,920

የጌዴኦ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት

3,460

የጋምቤላ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ

10,380

የሶማሌ ሕዝቦች ዴሞክራሲዊ ፓርቲ

3,460

የሐረሪ ብሔራዊ ሊግ  

3,460

የሐረሪ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓረቲ

6,920

የኢትዮጵያ ብሔራዊ አንድነት ፓርቲ

10,380

የጋሞ ዴሞክራሲያዊ ህብረት

6,920

የኢትዮጵያውያን አንድነት ዴሞክራሲያዊ ድርጅት

3,460

ድምር

3,242,870

 
     
     
       
   
       
 
 
 
This site is designed by Afrolink Studio
Copyright © 2005 National Electoral Board of Ethiopia. All rights reserved.